loading
ህጋዊ የጉዞ ፈቃድ ሳይኖራቸው ወደ ታንዛንያና ሊቢያ የገቡ 65 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ተመለሱ

አርትስ 10/04/2011
በታንዛንያ መንግስት ህጋዊ የጉዞ ፈቃድ ሳይኖራቸው የገቡ 231 ኢትዮጵያውያን ክሳቸው ተቋርጦ ምህረት አንዲያደርግላቸው በተደረገ ጥረትዛሬ  65ቱ ወደ ሀገራቸው ገብተዋል ፡፡

ቀሪዎቹ ከኢትዮጵያ አየርመንገድና ከዓለም አቀፍ የፍልሰት ድርጅት (አይ.ኦ.ኤም) ጋር በመተባበር  ወደሀገራቸው እንዲገቡ ይደረጋል ተብሏል፡፡

እንደውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ገለፃ ካይሮ የሚገኘው የኢትዮጲያ ኢምባሲ ሊቢያ ከሚኖሩ ሌሎች በጎ አድራጊኢትዮጵያውያን እና የዓለም አቀፍ የፍልሰት ድርጅት (አይ.ኦ ኤም) ጋር በመተባበር ዜጎች ወደሀገራቸው እንዲመሉ እያደረገ ነው፡፡

በተመሳሳይ ካርቱም ሱዳን የሚገኘው የኢትዮጲያ ኤምባሲ ከአገሪቱ ፖሊስ ጋር በመተባበር በህገወጥ አዘዋዋሪዎች ታግተው የነበሩ 15ኢትዮጵያውያንን ከታሰሩበት አስፈትቷል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *