loading
በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች እየተካሄዱ ነው

በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች እየተካሄዱ ነው

በሰሜን ሸዋ፣ ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ ምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ራያ ቆቦና ሌሎችም አካባቢዎች ሲከሰቱ የቆዩ የፀጥታ መደፍረሶችና በተለይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከሰሞኑ የተቀሰቀሰው ግጭት ያስከተለው ሞትና መፈናቀል ለሰልፎቹ መጠራት ምክንያት እንደሆኑ ታውቋል።

በሠላማዊ ሠልፈኞቹ ‹‹በአማራ ብሔር ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ይቁም፤ መንግሥት የዜጎችን ደህንነት ይጠብቅ›› የሚሉና የተለያዩ መልዕክቶች እየተላለፉ ነው።

የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት እንደገለጸዉ ሰላማዊ ሰልፉ በደብረ ታቦር፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ማርቆስ፣ መርዓዊና በሌሎች ከተሞች እየተካሄደ ይገኛል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *