loading
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሎሜ ወረዳ ሄሊኮፕተር ተከስክሶ የ18 ሰዉ ህይወት አለፈ፡፡ 

በዛሬዉ ዕለት ከረፋዱ 5፡30 የመከላከያ አየር ሃይል ሄሊኮፕተር 15 የመከላከያ ሰራዊት ባልደረቦች እና ሶስት ሲቪል ሰዎችን አሳፍሮ ከድሬዳዋ ቢሾፍቱ በመብረር ላይ እያለ ምስራቅ ሸዋ ዞን ሎሜ ወረዳ ኤጄሬ ቀበሌ ላይ ባጋጠመዉ መከስከስ አደጋ በበረራዉ ላይ የነበሩ ሁሉም ሰዎች ህይወት አልፏል። የአደጋዉ መንስኤም በመጣራት ላይ ይገኛል።
ከአቶ አዲሱ አረጋ ፌስ ቡክ ገጽ እንዳገኘነዉ፡፡ በዚህ አደጋ ህይወታችዉን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለወዳጅ ዘመዶቻቸዉ መፅናናትን እንመኛለን።

አርትስ 24/12/2010

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *