loading
በግሪክ በተቀሰቀሰ ሰደድ እሳት በርካቶች ህይወታቸውን አጥተዋል

በቦታው የተሰማሩ የነፍስ አድን ሰራተኞች እንዳሉት በዋና ከተማዋ አቴንስ አቅራቢያ በተከሰተው አደጋ እስካሁን 49 ሰዎች ሞተዋል፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው ከሟቾቹ መካከል ህጻናት የሚበዙ እንደሆነ ታምኗል፡፡ ሲ ኤን ኤን በዘገባው እንዳሰፈረው በግሪክ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2007 ወዲህ እንደዚህ ዓይነት የከፋ የእሳት አደጋ አጋጥሞ አያውቅም፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪ 156 ሰዎች የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል ተብሏል፡፡ ከነዚህ መካከል ደግሞ አስራ አንዱ […]

ሰሜን ኮሪያ የሮኬት ማስወንጨፊያ ጣቢያዎቿዋን ማፍረስ መጀመሯ ተሰማ

የሳተላይት ምስል እንደሚያሳየው ፒዮንግያንግ ቁልፍ የሮኬት ማስወንጨፊያ ጣቢያዎቿን እያፈረሰች መሆኗ ተረጋጋጧል፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው በተችዎቻቸው ዘንድ መቆሚያ መቀመጫ ላጡት ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ ትልቅ እፎይታ ነው፡፡ በሁኔታው የተደሰቱት ትራምፕም እኔ ያላልኩትን የሚያራግቡና የሀሰተኛ ወሬ የሚያናፍሱ በሰሜን ኮሪያ ድርጊት ተበሳጭቷል ለሚሉ ሁሉ ይሄው እኔ ደስተኛ ነኝ የሚል ጽሁፍ በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡ ይሁንና የአሜሪካ ባለስልጣናት ሰሜን ኮሪያ የምታፈርሰው […]

የሞሮኮ አየር መንገድ ለዛሬ ተይዘው የነበሩ በረራዎችን ለመሰረዝ ተገዷል

ምክንያቱ ደግሞ አብራሪዎቹ የስራ ማቆም አድማ በመምታታቸው ነው ብሏል የሞሮኮ ሮያል አየር መንገድ በድረ ገጹ ባሰራጨው ጽሁፍ፡፡ ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው አብራሪዎቹ ስራ ለማቆም ያስገደዳቸው ላቀረቡት የደሞዝና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ጥያቄ ከአሰሪ ድርጅታቸው አጥጋቢ መልስ አለማግኘታቸው ነው፡፡ በድርጅቱና በሰራተኞቹ መካከል ለወራት የዘለቀ ድርድር ቢደረግም መግባባት አልተቻለም ብለዋል የአብራሪዎች ማህበር አመራሮች፡፡ አየር መንገዱም ሰራተኞቹ ወደ ስራ ገበታቸው […]

የኪነ-ጥበብ ባለሞያዎች “መደመር በተግባር ” እያሉ ነው

የኪነጥበብ ባለሙያዎች የገቡትን ቃል ጠብቀው በጥቁር አንበሳ፣ በአለርት እና በቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታሎች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ሰጥተዋል፡፡ አርቲስቶቹ ከአድናቂዎቻቸው ጋር በመሆን “መደመር በተግባር” የሚል መሪ ቃል ይዘው ደም የመለገስ ተግባር ፈጽመዋል፡፡

መሪዎቹ ሜዳልያ ተሸለሙ

በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አልጋወራሽ ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ነኸያን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና ለኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ሰላም እንዲሰፍን ላበረከቱት አስተዋፅኦ የሀገሪቱን ፕሬዚዳንታዊ ሜዳሊያ ሸለሙ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በሀገር ውስጥና በውጭ የነበሩት ሲኖዶሶች በአንድ ሲኖዶስ ለመመራት ተስማሙ

ባለፉት 27 ዓመት በሁለት ሲኖዶስ ስትመራ የቆየችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ወደ አንድ ለማምጣት የሰላምና የእርቅ ጉባዔው በዋሸንግተን ደብረ ሀይል ቅዱስ ገብርዔል ቤተክርስቲያን ባለፈው እሁድ የሁለቱም ልኡካን አባቶች በተገኙበት የጋራ ጸሎትና የመክፈቻ መርሐ ግብር ተጀምሯል። በእስካሁኑ ውይይታቸው በአንድ ሲኖዶስ ለመመራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ነው የተነገረው። በተጨማሪም “የሀገር ቤት ሲኖዶስ” እና “ስደተኛ ሲኖዶስ” የሚባለውን ለማስቀረት ተስማምተዋል። ይህ […]

አሁን የኢትዮጵያ፣ ኤርትራና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የሶስትዮሽ ጉባኤ በአቡ ዳቢ እየተካሄደ ነዉ

በዚህ የሶስትዮሽ ጉባኤ ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አልጋወራሽ ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ነኸያን በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በሶስትዮሽ ውይይት ላይ የሶስቱ ሀገራት የኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲሁም ቀጠናዊ ጉዳዮች ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሆነው ተሾሙ

የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት በ5ኛ ዙር 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባዔው አቶ ሚሊዮን ማቲዮስን የክልሉ ርዕሰ መስተደሳድር አድርጎ ሾሟል። አቶ ሚሊዮን ቃለ መሃላ በመፈፀም ቀደም ሲል ክልሉን በርዕሰ መስተዳድርነት ሲያገለግሉ ከነበሩት አቶ ደሴ ዳልኬ ኃላፊነቱን ተረክበዋል። አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ በቅርቡ ክልሉን የሚያስተዳድረው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ደኢህዴን/ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው […]

ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስና ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዮስ ቀጣይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ፓትሪያሪክ ማን ይሆናል?

ይህ ጥያቄ ከእርቁ በኋላ የሚመለስ ቢሆንም ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ግን ለቢቢሲ አማርኛዉ እንደተናገሩት ከሁለቱ ፓትርያሪኮች መካከል የስልጣን መንበሩ ላይ መቀመጥ ያለበት የሚለው ጥያቄ ማነቆ ሆኖ የቆየ ቢሆንም እርሱን አሁን መፍታት ብዙም አይገድም ብለዋል። ብፁዕ አቡነ ማቲያስ የአስተዳደሩን ስራ እየሰሩ፤ አቡነ መርቆሪዮስን ደግሞ በመንበራቸው ሆነው ከአስተዳደሩ ስራ ግን ገለል እንዲሉ ስማቸውም በቅዳሴ እየተጠራ በሲኖዶሱም እየተገኙ እንዲቀጥሉ […]

በስብሰባ መሀል ዘና በሉና ተሸለሙ

ዛሬ ጠ/ሚኒስትሩ ከመምህራን ጋር የነበራቸው ቆይታ የቻይና ጉዞ ሽልማቶችም እንደነበሩት ሰምተናል፡፡ ዶ/ር አብይ ከጋበዟቸው እና ወደ መድረክ ከወጡት ስምንት መምህራን “ፑሽ አፕ” ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር የሰሩ እና ያልደከሙ ሦስት መምህራን ቻይና ለ 15 ቀን ስልጠና እንደሚሄዱ ተነግሯቸዋል፡፡ በወንዶቹ ሳያበቃ ለተመሳሳይ ውድድር ሲጋበዙ ተሸቀዳድመው የወጡ ከ36 በላይ ሴቶችም ለሁሉም የቻይና የጉብኝት ዕድል እንደተሰጣቸው ሰምተናል፡፡