loading
ትላንት በተከሰከሰዉ አዉሮፕላን ሊሳፈር የነበረዉና 2 ደቂቃ በማርፈዱ ከሞት የተረፈዉ ግሪካዊ እድለኛ እየተባለ ነዉ፡፡

 

ትላንት በተከሰከሰዉ አዉሮፕላን ሊሳፈር የነበረዉና 2 ደቂቃ በማርፈዱ ከሞት የተረፈዉ

ግሪካዊ እድለኛ እየተባለ ነዉ፡፡

ግሪካዊዉ አንቶኒዮ ማርቮፑሎስ ትላንት ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ለመጓዝ

በቦይንግ 737-8 ማክስ በበረራ ቁጥር ኢቲ 302 ትኬት ቆርጦ ነበር፡፡

ሆኖም አዉሮፕላኑ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ  ሲነሳ አንቶኒዮ ሁለት ደቂቃ አርፍዶ ነበር ፡፡እናም ትላንት በቢሾፍቱ አደጋ የደረሰበት አዉሮፕላን አመለጠዉና ከአደጋዉ ተረፈ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስኪያጅ አቶ አስራት በጋሻዉ ለአርትስ ቲቪ እንደተናገሩት እድለኛዉ  ሰዉየዉ በቀጣዩ በረራ  ወደ ናይሮቢ ሄዷል፡፡

 

 

 

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *