loading
አቶ ወዮ ሮባ የስኳር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ

አቶ ወዮ ሮባ የስኳር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ

አቶ ወዮ ሮባ አካኮ የስኳር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው መሾማቸውን ኮርፖሬሽኑ አስቋል ሲል ፋና ዘግቧል።

ኮርፖሬሽኑን ከታህሳስ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምረው ላለፉት ሦስት ወራት በተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚነት የመሩት አቶ ወዮ ሮባ ከመጋቢት 27 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሹመዋል።

አቶ ወዮ ወደ ስኳር ኮርፖሬሽን ከመጡበት ከ2004 ዓ.ም አንስቶ ለሰባት ዓመታት የኦፕሬሽንስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው የእርሻና የፋብሪካ ኦፕሬሽን ሥራዎችን መርተዋል።

ወደ ኮርፖሬሽኑ ከመምጣታቸው አስቀድሞም በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ማገልገላቸዉን  ሰምተናል

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *