loading
አቶ አህመድ ሽዴ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኢሶህዴፓ/ ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ።

የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኢሶዴፓ/ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባለፉት ሶስት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ጥልቅ ግምገማ ማጠናቀቁን ተከትሎ ነው አቶ አህመድ ሽዴ ሊቀ መንበር አድርጎ የመረጠው። የኢሶዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ አቶ አህመድ ሽዴን በሙሉ ድምጽ በሊቀ መንበርነት መምረጡም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኢሶዴፓ/ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባለፉት ሶስት ቀናት ስብሰባው በክልሉ ተፈጥሮ በነበሩው ሁኔታ […]

የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) ልኡክ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብቷል።

በግንባሩ ቃል አቀባይ አቶ አዳኒ አብዱልቃድር ሄርሞጌ የተመራው እና 3 አባላትን ያለው ልኡኩ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሚኒስትር ደኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ አቀባበል አድርገዋል። ወደ ሀገር የገባውን ልኡክ የመሩት አቶ አዳኒ አብዱልቃድር ሄርሞጌ፥ ግንባሩ ወደ ሀገር ቤት ለመግባት የወሰነው የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ […]

የህወሀት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን መቐለ በተካሄደው ሰልፍ ባስተላለፉት መልእክት “ያለን አማራጭ ተከባብሮ መኖር አልያም መበታተን” ማለታቸው ትግራይን ለመገንጠል ከሚል የመነጨ ሳይሆን የሀገሪቱ የፌደራል ስርአት እኩልነትን መሰረት ያደረገ መሆኑ ለመጠቆም የተነገረ ነዉ አሉ።

ህወሀት በዚህ ወር 13ኛ ድርጅታዊ ታሪካዊ የለውጥ ጉባኤ ያካሄዳል ተብሏል፡፡ ሊቀመንበሩ በጉባኤው እስካሁን የተደረጉት የለውጥ እንቅስቃሴዎች ወደተግባር ሊለውጥ የሚችል ብቁ አዲስ ትውልድ ወደ አመራርነት ይመጣል ብለዋል። ህወሓት ህገመንግስትን መሰረት አድርጎ ለሚደረግ የለውጥ ጉዞ ደጋፊ እንጂ እንቅፋት እንደማይሆን ዶክተሩ ተናግረዋል። በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ የሰጡት ሊቀመንበሩ ባለፉት አመታት በሀገሪቱ ከተመዘገቡ የልማት ስኬቶች በተጨማሪ በርካታ ጉድለቶች […]

መኢአድ አንቀጽ 39 እንዲሰረዝ ጠየቀ::

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አገር ለማፍረስ የተቀመጠ ነው ያለውን የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 39 እንዲሰረዝ ጥያቄ አቀረበ፡፡ ፓርቲውን ይህን ጥያቄ በይፋ ያቀረበው ሐሙስ ነሐሴ 3 ቀን 2010 ዓ.ም. ‹‹አገር ለማፍረስ የተቀመጠው አንቀጽ 39 የወለደው ችግር የበርካታ ዜጎችን ሕይወት እየቀጠፈ ይገኛል፤›› በማለት፣ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽሕፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡ […]

የኢንጂነር ስመኘው ቤተሰቦች የምርመራው ውጤት በምንፈልገው ፍጥነት እየሄደ አይደለም አሉ፡፡

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ላይ መኪናቸው ውስጥ ባልታወቀ ምክንያት ህይወታቸው አልፎ ከተገኘ ሁለት ሳምንታት አለፉ። ቢቢሲ እንደዘገበዉ የኢንጂነር ስመኘው ባለቤት የወ/ሮ ዕሙን ጌታሁን ታናሽ ወንድም የሆነው አካሉ ጌታሁን ”ሃዘናችን እጅግ ከባድ ቢሆንም እየበረታን ነው። ከቀብሩ ጀምሮ መንግሥት እየደገፈን ነው። ምንም ያወጣነው ወጪ የለም” ብሏል። አካሉ ጨምሮም […]

ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳን ጨምሮ 11 የፖሊስ አመራሮች በዋስ ቢለቀቁ እንደማይቃወም አቃቤ ህግ አስታወቀ

ሰኔ 16ቱ የመስቀል አደባባይ የድጋፍ ሰልፍ ላይ የአመራርነት ክፍተት አሳይተዋል ተብለው ምርምራ እየተካሄደባቸው የሚገኙት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ በዋስ ቢለቀቁ አቃቤ ህግ እንደማይቃወም ገለጸ፡፡ አቃቤ ህግ ምክትል ኮሚሽነሩን ጨምሮ ሌሎች 11 የፖሊስ አመራሮችም በዋስ ቢለቀቁ እንደማይቃወም አስታውቋል፡፡ የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎትም በጉዳዩ ውሳኔ ለመስጠት ለነገ ቀጠሮ መስጠቱ ተገልጿል፡፡ […]

አቶ ጀዋር መሀመድ በሻሸመኔ የተፈጸመዉን ድርጊት አወገዘ፡፡

በሻሸመኔ ከተማ ለሰዉ ህይወት መጥፋትና የአካል መጉደል ምክንያት የሆኑ ግለሰቦች ለህግ እንዲቀርቡም በፌስቡክ ገጹ ጠይቋል፡፡ አቶ ጀዋር የሻሸመኔ ህዝብ በታላቅ አክብሮትና ፍቅር ተቀብሎናል፤ነገርግን በከተማዋ ሊቀበለን የወጣዉ ህዝብ ቁጥር ከተጠበቀዉ በላይ በመሆኑና በህዝቡም መካከል ሀሰተኛ መረጃ በመሰራጨቱ ምክንያት የሰዎች ህይወት አልፏል፤ አካል ጉዳትም ደርስዋል ፤ በዚህም በጣም ማዘኑን ተናግሯል፡፡ ተጨባጭ ባልሆነ መረጃ ንጹህ የሆነ ሰዉን መጉዳት […]

በማሊ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በአንጻራዊነት ሰላማዊ ነበር ተባለ፡፡

ምርጫው በወቅቱ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት በኢብራሂም ቡበከር ኬታ እና በተቃዋሚው ሶውማሊያ ሲሴ መካከል ብርቱ ፉክክር ተካሂዶበታል ነው የተባለው፡፡ ዩሮ ኒውስ እንደዘገበው ሀገሪቱን እየመሩ ያሉት ኬታ ለሁለተኛ ጊዜ የማሸነፍ ዕድል እንዳላቸው እየተነገረላቸው ነው፡፡ በተፎካካሪነት እጩ ሆነው የቀረቡት ሲሴ በበኩላቸው ምርጫውን እንደሚያሸንፉ በልበ ሙሉነት ተናግረዋል፡፡ ሲሴ አያይዘውም ገዥው ፓርቲ የምርጫ ኮሮጆዎችን የራሱ ለማድረግ ሞክሯል የሚል ክስ ማቅረባቸው ተሰምቷል፡፡ […]

የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳላህና የፕሬዚዳንቱ አማካሪ የማነ ገብረአብ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ሞቃዲሾ መግባታቸዉን ኤርትሪያን ፕሬስ ዘግቧል፡፡

የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳላህና የፕሬዚዳንቱ አማካሪ የማነ ገብረአብ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ሞቃዲሾ መግባታቸዉን ኤርትሪያን ፕሬስ ዘግቧል፡፡ በዛሬው ዕለት ወደ ሞቃዲሾ ያቀናው በውጭ ጉዳዩ ሚኒስትሩ የተመራው ልዑክ በሁለትዮሽ እና በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተመራው ልዑክ ወደ ሞቃዲሾ ከማቅናቱ በፊት በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ቆይታ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ግብጽ አምስት ሰዎችን በእድሜ ልክ እስራት ቀጣች፡፡

የግብጽ ፍርድ ቤት የቀድሞውን የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ መሪ ሞሀመድ ባዲን ጨምሮ አምስት ሰዎች በእድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ ወስኖባቸዋል ተብሏል፡፡ አናዶሉ የዜና ወኪል እንደዘገበው አሁን ከአራት አጋሮቻቸው ጋር የእድሜ ልክ እስር የተፈረደባቸው ባዲ በ2013 ከተያዙ በኋላ በተናጠል ፍርድ ቤት ቀርበው የሞት ቅጣት ተወስኖባቸው ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ የቀድሞውን የአቅርቦት ሚኒስትር ባሰም ኡዳን በ15 ዓመት እንዲሁም ሌሎች 3 […]