loading
ጠቅላይ ሚነስትር አብይ አሕመድ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማቡዛን ተቀብለው አነጋገሩ።

ጠቅላይ ሚነስትር አብይ አሕመድ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማቡዛን ተቀብለው አነጋገሩ። ጠቅላይ ሚነስትር አብይ አሕመድ ዛሬ በጽ/ቤታቸው የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማቡዛን ተቀብለው ማነጋገራቸው ተሰምቷል። በህዳር ወር ኢትዮጵያን የጎበኙት የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፖሳ ጋር የተደረገው ውይይት ቀጣይ የሆነው የዛሬው ውይይት በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነትና ትብብር በማጥናከር ላይ ያተኮረ እንደነበር ከጠቅላይ […]

የኢትዮጵያ ክለቦች አሁንም የባህር ማዶ ተጫዋቾችን ማስፈረማቸውን ቀጥለውበታል

የኢትዮጵያ ክለቦች አሁንም የባህር ማዶ ተጫዋቾችን ማስፈረማቸውን ቀጥለውበታል ዘንድሮ ከከፍተኛ ሊግ ወደ ፕሪምየር ሊጉ በድጋሜ የተመለሰው ደቡብ ፖሊስ በኢትዮጵያ ልምድ ያላቸውን ናይጄሪያዊያን አጥቂዎች ፊሊፕ ዳውዝ እና ላኪ ሳኒ አስፈርመዋል፡፡ ቡድኑ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሁሉንም የጨዋታ መርሀ ግብሮች አከናውኖ በአምስት ነጥቦች 15ኛ ላይ ተቀምጧል፡፡ በአንጋፋ ተጫዋቾች የተሞላውን ደቡብ ፖሊስ ከአጥቂ ችግሩ ለመላቀቅ የሊጉ የልምድ ባለቤቶች ፊሊፕ […]

ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ እርሳቸውን ተክተው ከተሾሙት በመንግታቱ ድርጅት የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተወካይ ጋር መከሩ

ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ እርሳቸውን ተክተው ከተሾሙት በመንግታቱ ድርጅት የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተወካይ ጋር መከሩ፡፡ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በቅርቡ በተባበሩት መንግስታት ጽህፈት ቤት የአፍሪካ ህብረት ልዩ  ተወካይ ሆነው የተሾሙትን ሀና ሰርዋ በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ ልዩ ተወካይዋ ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅን በመተካት የተሾሙ ሲሆን የጉብኝታቸው ዓላማም ለፕሬዝዳንቷ የእንኳን ደስ አለዎ መልዕክት ለማስተላለፍና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከር ነው ተብሏል። […]

አማራ ክልላዊ መንግስት በክልሉ የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮች ታቅደው የሚደረጉ ሊሆኑ ይችላሉ የሚል ስጋት አለኝ አለ

የአማራ ክልላዊ መንግስት በክልሉ የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮች ታቅደው የሚደረጉ ሊሆኑ ይችላሉ የሚል ስጋት አለኝ አለ የክልሉ መንግስት ይህን ያለው በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጠው መግለጫ ነው፡፡ የአማራ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ አሰማኸኝ አስረስ በሰጡት መግለጫ በአብዛኞቹ የክልሉ አካባቢዎች የተሻለ ሰላም እና መረጋጋት ቢኖርም በአንዳንድ አካባቢዎች ግን የሰላም መደፍረስ ጎልቶ ይስተዋላል […]

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመች

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመች የውሃ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር የመግባቢያ ሰነዱን  የተፈራረመው ገልፍ የኤሌክትሪክ ትስስር ከተባለ የባህረ ሰላጤው አባል ሀገራት  የኃይል አቀርቦት ተቋም እና የዓለም አቀፉ የኃይል ትስስር ድርጅት ጋር ነው፡፡ ሰነዱ የሃይል አቅርቦትን መሰረት ያደረገ ጥናት ለማካሄድ የሚያስችል  ነው ተብሏል፡፡ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይም  የውሃ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር […]

ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘውን ጨምሮ 14 የሜቴክ የቀድሞ ሰራተኞች ተጨማሪ ከስ ተመሰረተባቸው

ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘውን ጨምሮ 14 የሜቴክ የቀድሞ ሰራተኞች ተጨማሪ ከስ ተመሰረተባቸው፡፡ አቃቤ ህግ ግለሰቦቹ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ከ28 ዓመታት በላይ የተገለገለባቸው አባይ ወንዝ እና አብዮት ከተባሉ ሁለት መርከቦች ግዢ ጋር በተያያዘ ተፈፅሟል ባላቸው የሙስና ወንጀሎች ነው የከሰሳቸው። ኮርፖሬሽኑ ምንም አይነት መርከብ የማስተዳደር ልምድ ሳይኖረው ሃላፊዎቹ ከሥልጣናቸው አልፈው  ተያያዥነት በሌለው ዘርፍ ለመሰማራት […]

ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ የምርጫ ድምፅ ቆጠራውን በድጋሜ እንድታካሂድ ተጠየቀች

ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ የምርጫ ድምፅ ቆጠራውን በድጋሜ እንድታካሂድ ተጠየቀች ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ያካሄደችው ፕሬዚዳንታዊ የምርጫ ፉክክር የድምፅ ቆጠራ ውጤት ይፋ ቢደረግም፤ በተፎካካሪዎች ዘንድ የተሳሳተ ነው መባሉን ተከትሎ የደቡብ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብ (ሳድክ)  የድምፅ ቆጠራውን በድጋሜ እንድታከናውን ጥሪ አቅርቦላታል፡፡ ኮንጎ ነፃነቷን ከተቀዳጀች ከ59 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ዴሞክራሲያዊ የስልጣን ሽግግር ማብሰሪያ  ይሆናል ብሎ ተስፋ የተጣበት ምርጫ […]

የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከጦርነት ይልቅ ጉርብትናችንን እናጠናክር እያሉ ነው

የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከጦርነት ይልቅ ጉርብትናችንን እናጠናክር እያሉ ነው የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሀመድ ጃቫድ ዛሪፍ ጎረቤት ሀገራት ጠንካራ ወደጅነት መፍጠር የሚሹ ከሆነ፤ ከጦር መሳሪያ ክምችት ፉክክር ይልቅ ውይይትን ሊያስቀድሙ ይገባል ብለዋል፡፡ ዛሪፍ ይህን  ያሉት በኢራቅ መዲና ባግዳድ ለተሰባሰቡ በመቶዎች ለሚቆጠሩ የኢራን እና ኢራቅ የቢዝነስ ተቋማትን ወክለው ለተገኙ ግለሰቦች ነው፡፡ ጃቫድ ዛሪፍ በንግግራቸው ጠንካራ […]

በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ማንችስተር ሲቲ አሸንፏል

በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ማንችስተር ሲቲ አሸንፏል የ22ኛ ሳምንት መርሀግብር የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻ ጨዋታ ትናንት ምሽት ኢቲሃድ ላይ በማንችስተር ሲቲ እና ወልቨርሃምፕተን ወንደረርስ መካከል ተካሂዷል፤ ወልቭስ ታላላቅ ክለቦችን ሲገጥም የሚያሳየውን ፉክክር ተከትሎ የምሽቱን ጨዋታ ተጠባቂ አድርጎት ነበር፡፡ በምሽቱ በተደረገው ግጥሚያ የፔፕ ጓርዲዮላው ሲቲ የ3 ለ 0 ድል በወልቭስ ላይ ተቀዳጅቷል፡፡ ድሉን ተከትሎ ከሊቨርፑል ጋር ያለውን […]

በቡራዩ  ከተማ  የእሳት አደጋ በንብረ ትላይ  ጉዳት አደረሰ፡፡

በቡራዩ  ከተማ  የእሳት አደጋ በንብረ ትላይ  ጉዳት አደረሰ፡፡ በቡራዩ ከተማ ለኩ ኩሌ ቀበሌ ከሌሊቱ 8 ሰአት ከሰላሳ ላይ ኢንተማ ትሬዲንግ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሻማ የሚያመርት ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ፋብሪካው ሙሉ ለሙሉ ወድሟል፡፡ የቡራዩ  ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር መርጊያ ሁንዴሳ ለአርትስ ቴሌቭዥን  እንደተናገሩት በእሳት አደጋው  ከፋብሪካው አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት  ሱቆች ተቃጥለዋል፡፡ በቃጠሎ አደጋው […]